2 ጥንት ገንዘብህ ያደረግሃትን ጉባኤ፣የዋጀሃትን የርስትህን ነገድ፣መኖሪያህ ያደረግሃትን የጽዮን ተራራ አስብ።
3 እርምጃህን ለዘላለሙ ባድማ ወደ ሆነው አቅና፤ጠላት በመቅደስህ ውስጥ ያለውን ሁሉ አበላሽቶአል።
4 ጠላቶችህ በመገናኛ ስፍራህ መካከል ደነፉ፤አርማቸውንም ምልክት አድርገው በዚያ አቆሙ።
5 በጫካ መካከል ዛፎችን ለመቍረጥ፣መጥረቢያ የሚያነሣ ሰው መሰሉ።
6 በእደ ጥበብ ያጌጠውን ሥራ ሁሉ፣በመጥረቢያና በመዶሻ ሰባበሩት።
7 መቅደስህን አቃጥለው አወደሙት፤የስምህንም ማደሪያ አረከሱ።
8 በልባቸውም፣ “ፈጽሞ እንጨቍናቸዋለን” አሉ፤እግዚአብሔር በምድሪቱ ላይ የተመለከበትን ስፍራ ሁሉ አቃጠሉ።