20 ኪዳንህን አስብ፤የዐመፅ መናኸሪያ በምድሪቱ ጨለማ ስፍራዎች ሞልተዋልና።
21 የተጨቈኑት አፍረው አይመለሱ፤ድኾችና ችግረኞች ስምህን ያመስግኑ።
22 አምላክ ሆይ፤ ተነሥ፤ ለዐላማህ ተሟገት፤ከንቱ ሰው ቀኑን ሙሉ እንደሚያላግጥብህ አስብ።
23 የባላጋራዎችህን ድንፋታ፣ዘወትር የሚነሣውን የጠላቶችህን ፉከራ አትርሳ።