13 “ምነው ሕዝቤ ቢያደምጠኝ ኖሮ፣እስራኤል በመንገዴ በሄደ ኖሮ፣
14 ጠላቶቻቸውን ፈጥኜ ባንበረከክኋቸው ነበር፤እጄን በባላጋራዎቻቸው ላይ ባነሣሁ ነበር።
15 እግዚአብሔርን የሚጠሉ በፊቱ ይርዳሉ፤ቅጣታቸውም እስከ ዘላለም የሚዘልቅ ነው።
16 እናንተን ግን ምርጡን ስንዴ አበላችኋለሁ፤ከዐለቱም ማር አጠግባችኋለሁ።”