17 ክፉዎች ተመልሰው ወደ ሲኦል ይወርዳሉ፤እግዚአብሔርን የሚዘነጉ ሕዝቦችም ሁሉ እንደዚሁ።
18 ችግረኞች ግን መቼም ቢሆን አይረሱም፤የድኾችም ተስፋ ለዘላለም መና ሆኖ አይቀርም።
19 እግዚአብሔር ሆይ ተነሥ፤ ሰውም አያይል፤አሕዛብም በፊትህ ይፈረድባቸው።
20 እግዚአብሔር ሆይ፤ ድንጋጤ አምጣባቸው፤ሕዝቦች ሰው ከመሆን እንደማያልፉ ይወቁ። ሴላ