4 ሺህ ዓመት በፊትህ፣እንዳለፈችው እንደ ትናንት ቀን፣እንደ ሌሊትም እርቦ ነውና።
5 እንደ ጐርፍ ጠርገህ ስትወስዳቸው፣ እንደ ሕልም ይበናሉ፤እንደ ማለዳ ሣር ታድሰው ይበቅላሉ፤
6 ሣሩም ንጋት ላይ አቈጥቍጦ ይለመልማል፤ምሽት ላይ ጠውልጎ ይደርቃል።
7 በቊጣህ አልቀናልና፤በመዓትህም ደንግጠናል።
8 በደላችንን በፊትህ፣የተሰወረ ኀጢአታችንንም በገጽህ ብርሃን ፊት አኖርህ።
9 ዘመናችን ሁሉ በቊጣህ ዐልፎአልና፤ዕድሜአችንንም በመቃተት እንጨርሳለን።
10 የዕድሜአችን ዘመን ሰባ ዓመት፣ ቢበዛም ሰማንያ ነው፤ከዚያ በላይ ከሆነም ድካምና መከራ ብቻ ነው፤ቶሎ ያልፋልና፤ እኛም ወዲያው እንነጒዳለን።