5 ተራሮች በእግዚአብሔር ፊት፣በምድርም ሁሉ ጌታ ፊት እንደ ሰም ቀለጡ።
6 ሰማያት ጽድቁን ያውጃሉ፤ሕዝቦችም ሁሉ ክብሩን ያያሉ።
7 ለተቀረጸ ምስል የሚሰግዱ፣በጣዖታትም የሚመኩ ሁሉ ይፈሩ፤እናንተ አማልክት ሁሉ፤ ለእርሱ ስገዱ።
8 እግዚአብሔር ሆይ፤ ስለ ፍርድህ፣ጽዮን ሰምታ ደስ አላት፤የይሁዳም ሴት ልጆች ሐሤት አደረጉ።
9 እግዚአብሔር ሆይ፤ አንተ በምድር ሁሉ ላይ ልዑል ነህና፤ከአማልክትም ሁሉ በላይ እጅግ ከፍ ያልህ ነህ።
10 እግዚአብሔርን የምትወዱ ክፋትን ጥሉ፤እርሱ የታማኞቹን ነፍስ ይጠብቃልና፤ከዐመፀኞችም እጅ ይታደጋቸዋል።
11 ብርሃን ለጻድቃን፣ሐሤትም ልባቸው ለቀና ወጣ።