3 በሙሉ ጨረቃ፣ በክብረ በዓላችን ዕለት፣በወሩ መግቢያ፣ ጨረቃ ስትወለድ መለከት ንፉ፤
4 ይህ ለእስራኤል የተሰጠ ሥርዐት፣የያዕቆብም አምላክ ድንጋጌ ነውና።
5 ሙሉ ለሙሉ ግብፅን ለቆ በወጣ ጊዜ፣ይህን ለዮሴፍ ደነገገለት፤በማላውቀውም ቋንቋ እንዲህ ሲል ሰማሁ፦
6 “ትከሻውን ከሸክም ገላገልሁት፤እጁንም ቅርጫት ከመያዝ አሳረፍሁ።
7 በመከራህ ጊዜ ጠራኸኝ፤ እኔም ታደግሁህ፤በነጐድጓድ መሰወሪያ ውስጥ መለስሁልህ፤በመሪባ ውሃ ዘንድ ፈተንሁህ። ሴላ
8 “ሕዝቤ ሆይ፤ ሳስጠነቅቅህ ስማኝ፤እስራኤል ሆይ፤ ምነው ብታደምጠኝ!
9 በአንተ ዘንድ ባዕድ አምላክ አይኑር፤ለሌላም አምላክ አትስገድ።